Bible

 

ማቴ 3

Studie

   

1-2 በዚያም ወራት መጥምቁ ዮሐንስ። መንግሥተ ሰማያት ቀርባለችና ንስሐ ግቡ ብሎ በይሁዳ ምድረ በዳ እየሰበከ መጣ።

3 በነቢዩ በኢሳይያስ። የጌታን መንገድ አዘጋጁ ጥርጊያውንም አቅኑ እያለ በምድረ በዳ የሚጮህ ሰው ድምፅ የተባለለት ይህ ነውና።

4 ራሱም ዮሐንስ የግመል ጠጉር ልብስ ነበረው፥ በወገቡም ጠፍር ይታጠቅ ነበር፤ ምግቡም አንበጣና የበረሀ ማር ነበረ።

5 ያን ጊዜ ኢየሩሳሌም ይሁዳም ሁሉ በዮርዳኖስም ዙሪያ ያለ አገር ሁሉ ወደ እርሱ ይወጡ ነበር፤

6 ኃጢአታቸውንም እየተናዘዙ በዮርዳኖስ ወንዝ ከእርሱ ይጠመቁ ነበር።

7 ዳሩ ግን ከፈሪሳውያን ከሰዱቃውያን ብዙዎች ወደ ጥምቀቱ ሲመጡ ባየ ጊዜ፥ እንዲህ አላቸው። እንተ የእፉኝት ልጆች፥ ከሚመጣው ቍጣ እንድትሸሹ ማን አመለከታችሁ?

8 እንግዲህ ለንስሐ የሚገባ ፍሬ አድርጉ፤

9 በልባችሁም። አብርሃም አባት አለን እንደምትሉ አይምሰላችሁ፤ እላችኋለሁና። ከነዚህ ድንጋዮች ለአብርሃም ልጆች ሊያስነሣለት እግዚአብሔር ይችላል።

10 አሁንስ ምሳር በዛፎች ሥር ተቀምጦአል፤ እንግዲህ መልካም ፍሬ የማያደርግ ዛፍ ሁሉ ይቈረጣል ወደ እሳትም ይጣላል።

11 እኔስ ለንስሐ በውኃ አጠምቃችኋለሁ፤ ጫማውን እሸከም ዘንድ የማይገባኝ ከእኔ በኋላ የሚመጣው ግን ከእኔ ይልቅ ይበረታል፤ እርሱ በመንፈስ ቅዱስ በእሳትም ያጠምቃችኋል፤

12 መንሹም በእጁ ነው፥ አውድማውንም ፈጽሞ ያጠራል፥ ስንዴውንም በጎተራው ይከታል፥ ገለባውን ግን በማይጠፋ እሳት ያቃጥለዋል።

13 ያን ጊዜ ኢየሱስ በዮሐንስ ሊጠመቅ ከገሊላ ወደ ዮርዳኖስ መጣ።

14 ዮሐንስ ግን። እኔ በአንተ ልጠመቅ ያስፈልገኛል አንተም ወደ እኔ ትመጣለህን? ብሎ ይከለክለው ነበር።

15 ኢየሱስም መልሶ። አሁንስ ፍቀድልኝ፤ እንዲህ ጽድቅን ሁሉ መፈጸም ይገባናልና አለው። ያን ጊዜ ፈቀደለት።

16 ኢየሱስም ከተጠመቀ በኋላ ወዲያው ከውኃ ወጣ፤ እነሆም፥ ሰማያት ተከፈቱ የእግዚአብሔርም መንፈስ እንደ ርግብ ሲወርድ በእርሱ ላይም ሲመጣ አየ፤

17 እነሆም፥ ድምፅ ከሰማያት መጥቶ። በእርሱ ደስ የሚለኝ የምወደው ልጄ ይህ ነው አለ።

   

Ze Swedenborgových děl

 

Scriptural Confirmations # 12

  
/ 101  
  

12. 10. Thou shalt call His name Jesus, He shall save the people from their sins (Matthew 1:21).

The wise men came to adore the infant Jesus, and that He would be born in Bethlehem according to Micah 5:1 (Matthew 2:1-6).

The wise men adored Him and brought Him gifts (Matthew 2:11).

Jesus said to John, It becometh us so to fulfil all the justice of God (Matthew 3:15).

Jesus said to the devil who was tempting, Thou shalt not tempt the Lord thy God; and again, Thou shalt adore the Lord thy God, and Him only shalt thou serve (Matthew 4:7, 10).

A ruler came and adored Jesus (Matthew 9:18).

He that receiveth Me receiveth Him that sent Me (Matthew 10:40).

All things are delivered unto Me by my Father, wherefore come ye all unto Me (Matthew 11:27-28).

They that were in the ship adored Jesus, saying, Of a truth Thou art the Son of God (Matthew 14:33). A woman of Canaan (Matthew 15:25), the disciples (Luke 24:52), a blind man (John 9:38), adored Him.

Multitudes glorified the God of Israel (Matthew 15:31). There is one Rabbi and one Master, that is, He teaches what is good and true (Matthew 23:8,10).

Of the sign of the coming of the Lord and of the consummation of the age (Matthew 24:1 to end).

Then shall there be wars and rumor, and they will say, I am the Christ; false prophets shall arise and seduce many; signifies the heresies in the first times, which were many (Matthew 24:5-14).

The women, running to Jesus, adored Him (Matthew 28:9).

He said, All power is given unto Me in heaven and on earth (Matthew 28:18; Psalms 8:6-7).

  
/ 101  
  

Thanks to the Swedenborg Foundation for their permission to use this translation.