Bible

 

ማቴ 12

Studie

   

1 በዚያን ጊዜ ኢየሱስ በሰንበት ቀን በእርሻ መካከል አለፈ፤ ደቀ መዛሙርቱም ተራቡና እሸት ይቀጥፉ ይበሉም ጀመር።

2 ፈሪሳውያንም አይተው። እነሆ፥ ደቀ መዛሙርትህ በሰንበት ማድረግ ያልተፈቀደውን ያደርጋሉ አሉት።

3-4 እርሱ ግን እንዲህ አላቸው። ዳዊትና ከእርሱ ጋር የነበሩት በተራቡ ጊዜ፥ እርሱ ያደረገውን፥ ወደ እግዚአብሔር ቤት እንደ ገባ ካህናትም ብቻ እንጂ እርሱና ከእርሱ ጋር የነበሩት ሊበሉት ያልተፈቀደውን የመሥዋዕቱን ኅብስት እንደ በላ አላነበባችሁምን?

5 ካህናትም በሰንበት በመቅደስ ሰንበትን እንዲያረክሱ ኃጢአትም እንዳይሆንባቸው በሕጉ አላነበባችሁምን?

6 ነገር ግን እላችኋለሁ፥ ከመቅደስ የሚበልጥ ከዚህ አለ።

7 ምሕረትን እወዳለሁ መሥዋዕትንም አይደለም ያለው ምን እንደሆነ ብታውቁስ ኃጢአት የሌለባቸውን ባልኰነናችሁም ነበር።

8 የሰው ልጅ የሰንበት ጌታ ነውና።

9 ከዚያም አልፎ ወደ ምኩራባቸው ገባ።

10 እነሆም፥ እጁ የሰለለች ሰው ነበረ፤ ይከሱትም ዘንድ። በሰንበት መፈወስ ተፈቅዶአልን? ብለው ጠየቁት።

11 እርሱ ግን። ከእናንተ አንድ በግ ያለው በሰንበት በጉድጓድ ቢወድቅበት፥ ይዞ የማያወጣው ሰው ማን ነው?

12 እንግዲህ ሰው ከበግ ይልቅ እንደምን አይበልጥም! ስለዚህ በሰንበት መልካም መሥራት ተፈቅዶአል አላቸው።

13 ከዚያም በኋላ ሰውየውን። እጅህን ዘርጋ አለው። ዘረጋትም፥ እንደ ሁለተኛይቱም ደህና ሆነች።

14 ፈሪሳውያን ግን ወጥተው እንዴት አድርገው እንዲያጠፉት ተማከሩበት።

15 ኢየሱስም አውቆ ከዚያ ፈቀቅ አለ። ብዙ ሰዎችም ተከተሉት፥ ሁሉንም ፈወሳቸው፥ እንዳይገልጡትም አዘዛቸው፤

16-17 በነቢዩ በኢሳይያስ የተባለው ይፈጸም ዘንድ እንዲህ ሲል።

18 እነሆ የመረጥሁት ብላቴናዬ፥ ነፍሴ ደስ የተሰኘችበት ወዳጄ፤ መንፈሴን በእርሱ ላይ አኖራለሁ፥ ፍርድንም ለአሕዛብ ያወራል።

19 አይከራከርም አይጮህምም፥ ድምፁንም በአደባባይ የሚሰማ የለም።

20 ፍርድን ድል ለመንሣት እስኪያወጣ፥ የተቀጠቀጠን ሸምበቆ አይሰብርም የሚጤስን የጥዋፍ ክርም አያጠፋም።

21 አሕዛብም በስሙ ተስፋ ያደርጋሉ።

22 ከዚህም በኋላ ጋኔን ያደረበትን ዕውር ዲዳም ወደ እርሱ አመጡ፤ ዕውሩም ዲዳውም እስኪያይና እስኪናገር ድረስ ፈወሰው።

23 ሕዝቡም ሁሉ ተገረሙና። እንጃ ይህ ሰው የዳዊት ልጅ ይሆንን? አሉ።

24 ፈሪሳውያን ግን ሰምተው። ይህ በብዔል ዜቡል በአጋንንት አለቃ ካልሆነ በቀር አጋንንትን አያወጣም አሉ።

25 ኢየሱስ ግን አሳባቸውን አውቆ እንዲህ አላቸው። እርስ በርስዋ የምትለያይ መንግሥት ሁላ ትጠፋለች፥ እርስ በርሱ የሚለያይ ከተማም ሁሉ ወይም ቤት አይቆምም።

26 ሰይጣንሰይጣንን የሚያወጣ ከሆነ፥ እርስ በርሱ ተለያየ፥ እንግዲህ መንግሥቱ እንዴት ትቆማለች?

27 እኔስ በብዔል ዜቡል አጋንንትን የማወጣ ከሆንሁ፥ ልጆቻችሁ በማን ያወጡአቸዋል? ስለዚህ እነርሱ ፈራጆች ይሆኑባችኋል።

28 እኔ ግን በእግዚአብሔር መንፈስ አጋንንትን የማወጣ ከሆንሁ፥ እንግዲህ የእግዚአብሔር መንግሥት ወደ እናንተ ደርሳለች።

29 ወይስ ሰው አስቀድሞ ኃይለኛውን ሳያስር ወደ ኃይለኛው ቤት ገብቶ እቃውን ሊነጥቀው እንዴት ይችላል? ከዚያም ወዲያ ቤቱን ይበዘብዛል።

30 ከእኔ ጋር ያልሆነ ይቃወመኛል፥ ከእኔ ጋርም የማያከማች ይበትናል።

31 ስለዚህ እላችኋለሁ፥ ኃጢአትና ስድብ ሁሉ ለሰዎች ይሰረይላቸዋል፥ ነገር ግን መንፈስ ቅዱስን ለሰደበ አይሰረይለትም።

32 በሰው ልጅ ላይ ቃል የሚናገር ሁሉ ይሰረይለታል፤ በመንፈስ ቅዱስ ላይ ግን የሚናገር ሁሉ በዚህ ዓለም ቢሆን ወይም በሚመጣው አይሰረይለትም።

33 ዛፍ ከፍሬዋ ትታወቃለችና ዛፍዋን መልካም፥ ፍሬዋንም መልካም አድርጉ፥ ወይም ዛፍዋን ክፉ ፍሬዋንም ክፉ አድርጉ።

34 እናንተ የእፉኝት ልጆች፥ ክፉዎች ስትሆኑ መልካም ለመናገር እንዴት ትችላላችሁ? በልብ ሞልቶ ከተረፈው አፍ ይናገራልና።

35 መልካም ሰው ከልቡ መልካም መዝገብ መልካም ነገርን ያወጣል፥ ክፉ ሰውም ከክፉ መዝገብ ክፉ ነገርን ያወጣል።

36 እኔ እላችኋለሁ፥ ሰዎች ስለሚናገሩት ስለ ከንቱ ነገር ሁሉ በፍርድ ቀን መልስ ይሰጡበታል፤

37 ከቃልህ የተነሣ ትጸድቃለህና ከቃልህም የተነሣ ትኰነናለህ።

38 በዚያን ጊዜ ከጻፎችና ከፈሪሳውያን አንዳንዶቹ መለሱና። መምህር ሆይ፥ ከአንተ ምልክት እንድናይ እንወዳለን አሉ።

39 እርሱ ግን መልሶ እንዲህ አላቸው። ክፉና አመንዝራ ትውልድ ምልክት ይሻል፥ ከነቢዩም ከዮናስ ምልክት በቀር ምልክት አይሰጠውም።

40 ዮናስ በዓሣ አንባሪ ሆድ ሦስት ቀንና ሦስት ሌሊት እንደ ነበረ፥ እንዲሁ የሰው ልጅ በምድር ልብ ሦስት ቀንና ሦስት ሌሊት ይኖራል።

41 ነነዌ ሰዎች በፍርድ ቀን ከዚህ ትውልድ ጋር ተነሥተው ይፈርዱበታል፤ በዮናስ ስብከት ንስሐ ገብተዋልና፥ እነሆም፥ ከዮናስ የሚበልጥ ከዚህ አለ።

42 ንግሥተ ዓዜብ በፍርድ ቀን ከዚህ ትውልድ ጋር ተነሥታ ትፈርድበታለች፤ የሰሎሞንን ጥበብ ለመስማት ከምድር ዳር መጥታለች፥ እነሆም፥ ከሰሎሞን የሚበልጥ ከዚህ አለ።

43 ርኩስ መንፈስ ግን ከሰው በወጣ ጊዜ፥ ዕረፍት እየፈለገ ውኃ በሌለበት ቦታ ያልፋል፥ አያገኝምም።

44 በዚያን ጊዜም። ወደ ወጣሁበት ቤቴ እመለሳለሁ ይላል፤ ቢመጣም ባዶ ሆኖ ተጠርጎ አጊጦ ያገኘዋል።

45 ከዚያ ወዲያ ይሄድና ከእርሱ የከፉትን ሰባት ሌሎችን አጋንንት ከእርሱ ጋር ይወስዳል፥ ገብተውም በዚያ ይኖራሉ፤ ለዚያም ሰው ከፊተኛው ይልቅ የኋለኛው ይብስበታል። ለዚህ ክፉ ትውልድ ደግሞ እንዲሁ ይሆንበታል።

46 ገናም ለሕዝቡ ሲናገር፥ እነሆ፥ እናቱና ወንድሞቹ ሊነጋገሩት ፈልገው በውጭ ቆመው ነበር።

47 አንዱም። እነሆ፥ እናትህና ወንድሞችህ ሊነጋገሩህ ፈልገው በውጭ ቆመዋል አለው።

48 እርሱ ግን ለነገረው መልሶ። እናቴ ማን ናት? ወንድሞቼስ እነማን ናቸው? አለው።

49 እጁንም ወደ ደቀ መዛሙርቱ ዘርግቶ። እነሆ እናቴና ወንድሞቼ፤

50 ሰማያት ያለውን የአባቴን ፈቃድ የሚያደርግ ሁሉ፥ እርሱ ወንድሜ እኅቴም እናቴም ነውና አለ።

   

Komentář

 

233 - Choose Life

Napsal(a) Jonathan S. Rose

Title: Choose Life

Topic: Salvation

Summary: We explore the benefits of going to heaven, which massively outweigh anything hell has to offer; yet the cost is high and deserves careful consideration.

Use the reference links below to follow along in the Bible as you watch.

References:
Deuteronomy 30:11, 19-20
Joshua 24:1, 13, 14
Luke 14:25, 32
Matthew 7:13-14
Judges 13
Luke 23
John 10:7
Matthew 18:1-10
John 8:34-36
Matthew 25:33-end
Psalms 103:20
Deuteronomy 32:30
Judges 5:31
Matthew 13:43
Luke 19:38
Isaiah 30:15; 32:17
Leviticus 26:36-37
2 Samuel 14:20
1 John 4:16
Psalms 84:10-11

Přehrát video
Spirit and Life Bible Study broadcast from 8/12/2015. The complete series is available at: www.spiritandlifebiblestudy.com

Bible

 

Luke 23

Studie

   

1 The whole company of them rose up and brought him before Pilate.

2 They began to accuse him, saying, "We found this man perverting the nation, forbidding paying taxes to Caesar, and saying that he himself is Christ, a king."

3 Pilate asked him, "Are you the King of the Jews?" He answered him, "So you say."

4 Pilate said to the chief priests and the multitudes, "I find no basis for a charge against this man."

5 But they insisted, saying, "He stirs up the people, teaching throughout all Judea, beginning from Galilee even to this place."

6 But when Pilate heard Galilee mentioned, he asked if the man was a Galilean.

7 When he found out that he was in Herod's jurisdiction, he sent him to Herod, who was also in Jerusalem during those days.

8 Now when Herod saw Jesus, he was exceedingly glad, for he had wanted to see him for a long time, because he had heard many things about him. He hoped to see some miracle done by him.

9 He questioned him with many words, but he gave no answers.

10 The chief priests and the scribes stood, vehemently accusing him.

11 Herod with his soldiers humiliated him and mocked him. Dressing him in luxurious clothing, they sent him back to Pilate.

12 Herod and Pilate became friends with each other that very day, for before that they were enemies with each other.

13 Pilate called together the chief priests and the rulers and the people,

14 and said to them, "You brought this man to me as one that perverts the people, and see, I have examined him before you, and found no basis for a charge against this man concerning those things of which you accuse him.

15 Neither has Herod, for I sent you to him, and see, nothing worthy of death has been done by him.

16 I will therefore chastise him and release him."

17 Now he had to release one prisoner to them at the feast.

18 But they all cried out together, saying, "Away with this man! Release to us Barabbas!"--

19 one who was thrown into prison for a certain revolt in the city, and for murder.

20 Then Pilate spoke to them again, wanting to release Jesus,

21 but they shouted, saying, "Crucify! Crucify him!"

22 He said to them the third time, "Why? What evil has this man done? I have found no capital crime in him. I will therefore chastise him and release him."

23 But they were urgent with loud voices, asking that he might be crucified. Their voices and the voices of the chief priests prevailed.

24 Pilate decreed that what they asked for should be done.

25 He released him who had been thrown into prison for insurrection and murder, for whom they asked, but he delivered Jesus up to their will.

26 When they led him away, they grabbed one Simon of Cyrene, coming from the country, and laid on him the cross, to carry it after Jesus.

27 A great multitude of the people followed him, including women who also mourned and lamented him.

28 But Jesus, turning to them, said, "Daughters of Jerusalem, don't weep for me, but weep for yourselves and for your children.

29 For behold, the days are coming in which they will say, 'Blessed are the barren, the wombs that never bore, and the breasts that never nursed.'

30 Then they will begin to tell the mountains, 'Fall on us!' and tell the hills, 'Cover us.'

31 For if they do these things in the green tree, what will be done in the dry?"

32 There were also others, two criminals, led with him to be put to death.

33 When they came to the place that is called The Skull, they crucified him there with the criminals, one on the right and the other on the left.

34 Jesus said, "Father, forgive them, for they don't know what they are doing." Dividing his garments among them, they cast lots.

35 The people stood watching. The rulers with them also scoffed at him, saying, "He saved others. Let him save himself, if this is the Christ of God, his chosen one!"

36 The soldiers also mocked him, coming to him and offering him vinegar,

37 and saying, "If you are the King of the Jews, save yourself!"

38 An inscription was also written over him in letters of Greek, Latin, and Hebrew: "THIS IS THE KING OF THE JEWS."

39 One of the criminals who was hanged insulted him, saying, "If you are the Christ, save yourself and us!"

40 But the other answered, and rebuking him said, "Don't you even fear God, seeing you are under the same condemnation?

41 And we indeed justly, for we receive the due reward for our deeds, but this man has done nothing wrong."

42 He said to Jesus, "Lord, remember me when you come into your Kingdom."

43 Jesus said to him, "Assuredly I tell you, today you will be with me in Paradise."

44 It was now about the sixth hour, and darkness came over the whole land until the ninth hour.

45 The sun was darkened, and the veil of the temple was torn in two.

46 Jesus, crying with a loud voice, said, "Father, into your hands I commit my spirit!" Having said this, he breathed his last.

47 When the centurion saw what was done, he glorified God, saying, "Certainly this was a righteous man."

48 All the multitudes that came together to see this, when they saw the things that were done, returned home beating their breasts.

49 All his acquaintances, and the women who followed with him from Galilee, stood at a distance, watching these things.

50 Behold, a man named Joseph, who was a member of the council, a good and righteous man

51 (he had not consented to their counsel and deed), from Arimathaea, a city of the Jews, who was also waiting for the Kingdom of God:

52 this man went to Pilate, and asked for Jesus' body.

53 He took it down, and wrapped it in a linen cloth, and laid him in a tomb that was cut in stone, where no one had ever been laid.

54 It was the day of the Preparation, and the Sabbath was drawing near.

55 The women, who had come with him out of Galilee, followed after, and saw the tomb, and how his body was laid.

56 They returned, and prepared spices and ointments. On the Sabbath they rested according to the commandment.